ዜናዎች

ሽመልስ በቀለ ለሌላኛው የግብጽ ክለብ ፊርማውን አኖረ !

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አማካይና በግብፅ ሊግ የተሳካ ጊዜ እያሳለፈ የሚገኘው ሽመልስ በቀለ ከግብፁ ክለብ ምስር ኤል መቃሳ ጋር በመለያየት ለሌላኛው የግብፅ ክለብ ኤል ጎውናን ለቀጣይ ዓመት ለመጫወት ፊርማውን ብሔራዊ ቡድኑን ከመቀላቀሉ በፊት አኑሯል ። በግብፅ ፕሪሚየር ሊግ ለተከታታይ አመታት ድንቅ ብቃቱን በማሳየት ዘንድሮ በ 11 ጎሎች አዲስ ታሪክ ያስመዘገበው ሽመልስ በቀለ በቀጣይም ዓመት በሌላኛው የግብፅ […]

ዜናዎች

ዋልያዎቹ አክራ ደርሰዋል- ጨዋታው የቀጥታ ሽፋን ያገኛል!

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአምስት ሰዓታት በረራ በኋላ አክራ አየር ማረፊያ የደረሱ ቢሆንም ለኢንተርናሽናል በሪራ ከኢትዮጵያ የሰጡት የኮቪድ ምርመራ ውጤት አክራ ላይ ባለመቀበላቸው ቡድኑ ዳግም ምርመራ አድርጎል። በዚህም ለእያንዳንዱ ተጨዋች ከ6800 የኢትዮጵያ ብር በላይ ተከፍሎ የኮቪድ ምርመራ ማድረጋቸው ተሰምቷል። በተያያዘ መረጃ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጋና አቻው ጋር ዓርብ ምሽት በ 4:00 የሚደርጉት የ2022 የዓለም ዋንጫ ቅድመ […]

ዜናዎች

የአማካይ መስመር ተጫዋቹ ከጉዳት መልስ ዋልያዎቹን በቀጣይ ሳምንት ይቀላቀላል !

በኢትዮጵያ አዘጋጅነት በባህርዳር በተካሄደው የሴካፋ ከ 23 አመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ውድድር የብሄራዊ ቡድኑ ሁለተኛ አምበል የነበረው እና በዋናው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ልምምድ ላይ ጉዳት አጋጥሞት የነበረው ሀብታሙ ተከስተ ከጉዳቱ ሙሉ ለሙሉ ማገገሙ ታውቋል።  በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባል የሆነውና ከሁለት ሳምንት በፊት በልምምድ ሜዳ ከሌላው የብሔራዊ ቡድኑ ተጨዋች ጋር በደረሰ ንክኪ ጉዳት አጋጥሞት የነበረው […]

ዜናዎች

” ሰባት ቋሚ ተሰላፊዎቻችን በብሔራዊ ቡድን በመሆናቸው በዛሬው ጨዋታ ባይሰለፉም ጨዋታው ለቀሪ አባሎቻችንን መልካም አጋጣሚ ነው ” – አሰልጣኝ ስዩም ከበደ

ለአፍሪካ ቻምፒዮንስ ሊግ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ከሳምንታት በኋላ ኢትዮጵያን በመወከል የሚያደርገው የአሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፋሲል ከነማ ለዝግጅቱ ይረዳው ዘንድ የአቋም መለኪያ ጨዋታ ዛሬ ከቀኑ በ10:00 ሰዓት በአሰልጣኝ ሰርዲዮቪች ሚሉቲን  ሚቾ ከሚሰለጥነው ዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድን ጋር በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል። የ2013 የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮናው የፋሲል ከነማ ስፓርት ክለብ በቀጣይ ለሚጠብቀው ሀገራዊ እና […]

ዜናዎች

-ኢትዮዽያዊው አማካይ ሽመልስ በግብፅ ቆይታው የጎል ሪከርዱን አሻሻለ ! – የሱዳን የጎል ሪከርዱ እስካሁን አልተነካም!

በግብፅ ፕሪሚየር ሊግ ዘንድሮ ድንቅ ብቃቱን በማሳየት ላይ የሚገኘው ኢትዮዽያዊው ሽመልስ በቀለ በዚህም ሳምንት የተለየ የሆነውን ጎል አስቆጥሯል። በግብፅ ፕሪምየር ሊግ ከከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎች አንዱ የሆነው የአማካይ ስፍራው ሽመልስ በቀለ በትላንት ምሽቱ ጨዋታ ክለቡ ምስር ለል መቃሳ በአል ሞካውሎን 3 ለ 2 ሽንፈን ቢያስተናግድም ሽመልስ በግብፅ ሊግ ቆይታው ያስቆጠረውን የጎል መጠን አሻሽሏል። ኢትዮጵያዊው አማካይ ሽመልስ […]

አፍሪካ ዜናዎች

– ዓፄዎቹ አዲስ እና ነባር ተጨዋቾቹን በመያዝ ለአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ዝግጅታቸውን በባህር ዳር ቀጥለዋል !

በአፍሪካ ቻምፒየንስ ሊግ ኢትዮጵያን የሚወክለው ፋሲል ከነማ ከሱዳኑ አሊሂላል ጋር ከጳግሜ 5 እስከ መስከረም 2/2014 ዓ.ም ባሉት ቀናቶች በሜዳው ባህር ዳር አለማቀፍ ስታዲየም የመጀመሪያ ዙር የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን እንደሚያደርግ የወጣው እጣ ድልድል ያመለክታል። ለዚህ ዝግጅትም ዓፄዎቹ ከቀናት በፊት አዲስ ያስፈራማቸውን እና በ2013 ሻምፒዮና የነበሩትን ነባር ተጨዋቾቹን በመያዝ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ  ዝግጅታቸውን በባህር ዳር እያደረጉ እንደሚገኝ […]

ዜናዎች

ዋልያዎቹ በፊፋ የደረጃ ሰንጠረዥ ከዓመታት ቆይታ በኋላ ከፍተኛ መሻሻል አሳዩ!

ዛሬ ይፋ በሆነው የፊፋ ወርሃዊ የአገራት ደረጃዎች መሰረት ኢትዮጵያ የወንዶች ብሔራዊ ቡድኑ ከዓመታት ቆይታ በኋላ በደረጃ ሰንጠረዥ ከፍ  ማለቱን  ቀጥሏል።   በኮሮና ምክንያት የአገራት ውድድር መቋረጡን ተከትሎ በ2019/2020 መቋረጥ አጋጥሞት የነበረው ወርሃዊ የደረጃ ሰንጠረዥ ባለፈው ዓመት ውድድሮች መቀጠላቸውን ተከትሎ ፊፋ የዓለም አገራት ወርሀዊ የደረጃ ሰንጠረዥን ይፋ ማድረጉን ቀጥሏል። በዚህም መሰረት  በወርዊው የደረጃ ሰንጠረዥ ዋልያዎቹ በአፍሪካ ዋንጫ […]

አፍሪካ ዜናዎች

– የአፍሪካ እግርኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ለፋሲል ከነማ እና ለኢትዮጵያ ቡና የሰጠው ቀነ ገደብ እሁድ ይጠናቀቃል !

የአፍሪካ እግር ኳስ የበላይ አካል (ካፍ) እ.ኤ.አ በ2021/2022 በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒየንስ ሊግ እና በኮንፌዴሬሽን ካፕ የሚሳተፉት ክለቦች ላይ ተጨዋቾቻቸውን አስመልክቶ የሰጠው ቀነ ገደብ የአምስት ቀናት የጊዜ ገደብ ብቻ ቀርቶቷል። በ2013 የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮናው ፋሲል ከነማ  እና የ2013 ዓ.ም በሁለተኝነት ያጠናቀቀው ኢትዮዽያ ቡና በአፍሪካ መድረክ የሚወክሉት እንደሆነ ይታወቃል። በአፍሪካ ክለቦች ሻምፒየንስ ሊግና በኮንፌዴሬሽን ካፕ […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

– በቶኪዮ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድኑ በመዝጊያው ስነስርዓት በባህል ልብስ በዛ ብሎ ታይተዋል ! – መቼ ይገባሉ ? አቀባበል ? እነማን ነበሩ? ከ250 ሚሊየን ብር በጀት ሆኗል ?

  የቶኪዮ 2020 ኦሎምፒክ በደማቅ የመዝጊያ ስነ-ስርአት ተጠናቋል። በ2020 የቶክዮ የመዝጊያ ስነ-ስርአት ሲጠናቀቅም በመክፈቻው ላይ ያልታየው  በመዝጊያ ሥነ ሥርዓቱ ላይ  የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ  የልዑካን ቡድን በባህል ልብስ በስታዲየም ውስጥ በዛ ብሎ ታይል።  ኢትዮዽያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ በ4 ስፖርቶች ያገኘችው 4 ሜዳሊያዎች ብቻ ነበር (1 ወርቅ ፤ 1 ብርና ሁለት የነሐስ ሜዳሊያዎች) ከአፍሪካ 3ኛ ከዓለም 56ኛ ደረጃ አጠናቃለች። […]

ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

ሙጂብ ቃሲም ወደ አልጀሪያ ሊያመራ ነው ! ጌታነህ ወደ ፋሲል ከነማ?

የ2013 ሻምፒዮን ፋሲል ከነማ ከጎል አዳኛቸው ሊለያዪ  ሙጂብ ቃሲም  ወደ አልጄሪያው  Jeunesse Sportive de Kabylie Fc (JSK) ሊያመራ መሆኑ ተሰምቷል ።  ኢትዮኪክ ጉዳዮን ከሰማንበት ጊዜም ጀምሮ ስለጉዳዩ ሙጂብ ቃሲምን ጠይቀን ምላሹን እየጠበቅን ሲሆን  ሙጂብን እንዳገኘነው ምላሹን የምናሠማ ይሆናል። እንደ መረጃው  ከሆነ ግን የሙጂብ የአልጄሪያው ዝውውር መሣካቱ ተሰምቷል።  በተጨማሪም የፋሲል ከነማ አመራሮች ብዙም ግልጽ ባልሆነ መንገድ […]