ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

” ዘንድሮ እንተርፋለን፣ አንተርፍምም ለማለት ይከብዳል ፤ ኳስ ነውና ምን እንደሚፈጠር አብረን እናያለን” ➖ተመስገን ደረሰ (ጅማ አባጅፋር)

የጅማ አባጅፋሩ ተመስገን ደረሰ በቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬም ፈጣኗን ጎል አስቆጥሯል። ተመስገን በሊጉ ስድስት ጎሎችያስቆጠረ ሲሆን የዛሬዋን ጨምሮ ሁለት ጎሎች ፈጣን ጎሎች ሆነው ተመዝግበዋል። ተመስገን ከጨዋታ በኃላ ከሱፐር ስፓርት ቆይታ አድርጓል። ዘንድሮ የውድድር ዓመት ቡድኑን ወጥ ያልሆነ ውጤት ይታይበታል። ስለዛሬው ጨዋታ ያለው አመለካከት? ” ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር እንደመጫወታችን ጨዋታው በጣም ከባድ ነበር። እኛም ግምት ሰጥተን […]

ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

” ትልቅ ነገር አቅደናል፣ ከአንደኛ አስከ ሦስተኛ ለመውጣት ፣አይከብደንም ያንንም እናሳካዋለን ” ➖ወንድማገኝ ኃይሉ

በ20ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ የምሽቱ ጨዋታ ሃዋሳ ከተማ ከ ባህርዳር ከተማ ያደረጉት ጨዋታ የሃዋሳ አማካይ ወንድማገኝ ኃይሉ ባስቆጠረው ብቸኛ ጎል ጨዋታው ተጠናቋል።ከጨዋታው በኋላ ወንድማገኝ ከሱፐር ስፓርት ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል። ጎሉን ስታስቆጥር የነበረህ ስሜት ? “በጣም ደስ ብሎኛል በጣም ደስ ያለኝ ደግሞ ማሸነፊያ ጎል ሆኖ ጨዋታው ካለቀ በኃላ ውጤቱን ስናይ በጣም ነው ደስ ያለኝ […]

ዜናዎች

” ወላይታ ድቻን ከፍ ማድረግ ነው ዘንድሮ የምንፈልገው፤ ያሳደገን ቡድንም ስለሆነ ” -ቸርነት ጉግሳ

የወላይታ ድቻ በጥሩ አቋም ላይ ከሚገኙ ተጨዋቾች አንዱ ቸርነት ጉግሳ ነው። ቸርነት ቡድኑ የዛሬውን ጨዋታ በአቻ ውጤት እንዲወጣ ሁለተኛ ጎል በ83ኛ ደቂቃ አስቆጥሯል።ከጨዋታው በኋላ ቸርነት ከሱፐር ስፓርት ጋር ቆይታ አድርጓል። የዘንድሮው የውድድር ዓመት እንዴት እየሄደ ነው እየሄደ ያለው ? “የዘንድሮው የውድድር ዓመት አጀማመሬ አሪፍ ነበር መሃል አካባቢ ትንሽ የመቀዛቀዝ ነበር ከጉዳት ጋር ነገር ግ አሁን […]

ዜናዎች

የወላይታ ድቻ ተጨዋቾቹ ከኮቪድ ነፃ ናቹ ሲባሉ አሰልጣኝ ዘላለም በዛሬው ጨዋታ አይኖርም !

በቤትኪንግ የ19ኛው ሳምንት ጨዋታ ወላይታ ድቻ አንድም ተቀያሪ ተጨዋች ሳይኖረው በ11 ተጨዋቾች ብቻ ሃዋሳ ከተማ ገጥሞ ጨዋታን በ3 ለ 2 ተሸናፊነት ማጠናቀቁ ይታወሳል። ከቀናት በፊት ተቀያሪ ተጨዋቾች ያልነበረው እና  በአጥቂ ቦታ ላይ ግብ ጠባቂዎቹ መክብብ እና አብነት   ያሰለፈው ወላይታ ድቻ በዛሬው የምርመራ ውጤት ደግሞ ከእዮብ አለማየሁ ውጪ ሁሉም የወላይታ ዲቻ ተጫዋቾች ከኮቪድ ነፃ ናችሁ ሲባሉ […]

አፍሪካ ዜናዎች

በልምምድ ሜዳ ህይወቱ በድንገት ያለፈው የአማካይ ቦታ ተጨዋች !

የጊኒ እግር ኳስ ዛሬ በሀዘን ውስጥ ይገኛል። ለጊኒ የዋናው ሊግ HAFIA FC ክለብ በአማካይ ቦታ ተጨዋች የነበረው ወጣት ሞሀመድ ላቲጌ ካማራ የተባለው ተጨዋች በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቱ አልፏል።የ24 አመቱ ተጨዋች ሞሃመድ ላቲጌ ህይወት በድንገት ያለፈው ዛሬ ረፋድ በኖንጎ ከቡድን ጓደኞቹ ጋር መደበኛ ልምምድ እየሰሩ ሳለ ድንገት ጥሩ ያልሆነ ስሜት ተሰምቶት ብዙም ሳይቆይ ራሱን ስቶ ሲወድቅ የቡድን […]

ዜናዎች

➖◾ ቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ አስገራሚው አጋጣሚዎች – እውነታዎች ◾➖

በቤትኪንግ ፕሪምየር አስገራሚው አጋጣሚዎች በ19ኛው  ሳምንትም ታይትዋል ። በ19ኛው ሳምንት በአጠቃላይ 16 ኳሶች ከመረብ ተዋህደዋል። በብዛት ጎሎች ተቆጥረውበት የተጠናቀቀው ጨዋታ ወላይታ ድቻ ከሃዋሳ ከተማ ያደረጉት ሲሆን ሃዋሳ 3 ለ 2 አሸንፏል። የሰበታ ከተማው ኦስይ ማወሊ የ19ኛው ሳምንት ሁለት ጎሎች ያስቆጠረ ብቸኛው ተጨዋች ነው። በ19ኛው ሳምንት ፈጣን ጎል ያስቆጠረው ሙጂብ ቃሲም ሲሆን በ3ኛው ደቂቃ ቡድኑ ሲዳማ […]

ዜናዎች

“የትላንቱ  የለቆሶ ስሜት ያለፍኩበትን የትግል ወራቶች ያስታወሰ ስሜት ነበር ማለት እችላለሁ ” -አሰልጣኝ ስዩም ከበደ(ፋሲል ከነማ)

የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ትላንት ቡድናቸው የሊጉን ዋንጫ ግስጋሴውን ያቀናበትን ሶስት ነጥብ ይዞ ከወጣ በኋላ ተጨዋቾቹ በደስታ ሲዘምሩ እሳቸው በደስታ ሲያነቡ ተስተውሏል። የ19ኛው ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ሲዳማ ቡናን 2 ለ1 ካሸነፈ በኃላ በመልበሻ ቤት አሰልጣኝ ስዪም ከበደ እጅጉን ስቅስቅ ብለው አልቅሰዋል። የዓፄዎቹ ዋና አሰልጣኝ ስዪም ከበደ ለቅሷቸው የደስታ ቢሆንም አብሮ የተያያዘ ነገር […]

ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

“የደርቢ ጨዋታው ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ፤ደጋፊዎቻችንን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት እፈልጋለሁ ” ➖አስቻለው ታመነ

በ19ኛው ሳምንት የሸገር ደርቢ ጨዋታ ለቅዱስ ጊዮርጊስ የማሻነፊዋን ጎል አስቻለው ታመነ ጨዋታው በተጀመረ በ12ኛው ደቂቃ በጭንቀት አስቆጥሮ ጨዋታው በአስቻለው ብቸኛ ጎል ተጠናቋል። ከጨዋታው በኋላ አስቻለው ታመነ ከሱፐር ስፖርት ጋር ቆይታ አድርጓል። በደርቢ ጨዋታ ጎል በማስቆጠሩ የተሰማው ስሜት ? ” ስሜቱ በጣም ደስ የሚል ነው። በእኔ ጎል ማሸነፋችን ደግሞ በጣም ደስ ብሎኛል ። በጣም ደስ የሚለው […]

ዜናዎች

“በሬውን ከጥጃ የሚለው ፕሪንስፕል ተግባራዊ አድርገን ነው ሻምፒዮና እንዲሁም ወደ ቤትኪንግ የተመለስነው ” ➖አሰልጣኝ እስማኤል አቡበከር (ዊሀ)

የአዲስ አበባ ከተማ እግር ኳስ ቡድን ለቀጣዩ ዓመት ወደ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግን በወጣቱ አሰልጣኝ እስማኤል አቡበከር (ዊሀ) ተመልሷል።ወጣቱ አሰልጣኝ እስማኤል አቡበከር ትውልድ እና ዕድገቱ ልደታ በተለምዶ “ቤሪሞ” ሜዳ በሚባለው አካባቢ ሲሆን የዘጠናዎቹ ኮከብ በፈጣን አጥቂነቱም ብዙዎች ያስታውሱታል። በተለይም በብሔራዊ ቡድን ከታዳጊ እስከ ዋናው ቡድን መጫወት የቻለ ሲሆን በ1990 ዓ.ም ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢያመራም በጊዜው በጉዳት […]

ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

“ለቀጣይ ጨዋታ ሲዳማ ቡና አሸንፈን ሦስት ነጥብ ለማምጣት ጥረት እናደርጋለን “ አሰልጣኝ ዘማርያም ወልደጊዮርጊስ (ድሬዳዋ ከተማ)

የቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ 19ኛ ሳምንት ጨዋታ  የድሬደዋ ከተማ ከባህርዳር አቻው ጋር አንድ ለ አንድ ተለያይተዋል። ከጨዋታው በኃላ የድሬደዋው አሰልጣኝ ዘማርያም ወልደጊዮርጊስ    ከሱፐር ስፖርት ጋር ቆይታ አድርገዋል። የሚገባውን ውጤት አግኝቷል ቡድንህ ? ጥሩ ነበርን። ባህርዳር ከነማ ያው ኳስን መስርቶ አድርጎ ነው ሚጫወተው። ግን ሜዳቸው ላይም ብዙ ይቆያሉ። ስለዚል እኛ በመልሶ ማጥቃት ጎል የማጎባት ዕድል ፈጥረን […]