Sunday Mutuku
አፍሪካ ዜናዎች

“የኢትዮጵያ ሊግ ከአውሮፓው ሊግ ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ በኢትዮጵያ ሊግ መጫወቴ ለእኔ ትልቅ ኩራት ነው” – ኬኒያዊው ሰንደይ ሙቱኩ

ኬኒያዊው ሰንደይ ሙትኩ በመሃል ተከላካይና አማካኝ ስፍራ የሚጫዎት ሁለገብ ተጨዋች ነው። ተጨዋቹ በኢትዮዽያ ሊግ አምስት የውድድር ጊዜያት እና ለሶስት ክለቦች ተጫውቶ  አሳልፏል። ሰንደይ ሙትኩ ወደ ኢትዮዽያ ሊግ ከመምጣቱ በፊት በሀገሩ ኬኒያ እ.ኤ.አ 2015 ላይ ለ3ኛ ዲቪዚዮኑ ያታ ኮምቦይን እና ለ2ኛ ዲቪዚዮኑ ካካሜጋ ሆምቦይዝ ክለብ አምበል ሆኖ ተጫውቶል።   በኃላም ኤ.ኤ.አ 2017 ወደ ኢትዮጵያ ሊግ በመምጣት ለሲዳማ […]

አፍሪካ ዜናዎች

በልምምድ ሜዳ ህይወቱ በድንገት ያለፈው የአማካይ ቦታ ተጨዋች !

የጊኒ እግር ኳስ ዛሬ በሀዘን ውስጥ ይገኛል። ለጊኒ የዋናው ሊግ HAFIA FC ክለብ በአማካይ ቦታ ተጨዋች የነበረው ወጣት ሞሀመድ ላቲጌ ካማራ የተባለው ተጨዋች በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወቱ አልፏል።የ24 አመቱ ተጨዋች ሞሃመድ ላቲጌ ህይወት በድንገት ያለፈው ዛሬ ረፋድ በኖንጎ ከቡድን ጓደኞቹ ጋር መደበኛ ልምምድ እየሰሩ ሳለ ድንገት ጥሩ ያልሆነ ስሜት ተሰምቶት ብዙም ሳይቆይ ራሱን ስቶ ሲወድቅ የቡድን […]

አፍሪካ ዜናዎች

ጋናዊው የመሀል ዳኛ ቻርለስ ቡሉ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ !

በአቢጃን ትላንት የተደረገውን የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን ከኢትዮጵያ አቻቸው ያደረጉትን የአፍሪካ ዋንጫ የመጨረሻ ጨዋታ በመሀል ዳኝነት የመሩት የጋናዊው ዳኛ ቻርለስ ቡሉ በ81ኛው ደቂቃ ባጋጠማቸው ድንገተኛ ህመም ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸው ይታወሳል።የትላንቱ የኮትዲቯር እና የኢትዮጵያ ጨዋታ ሊጀመር 3 ሰዓት ሲቀረው የእለቱ ዋና ዳኛ ጋናዊው ዳንኤል በኮቪድ መያዛቸውን ተከትሎ የጨዋታው ኮሚሽነር ከካፍ ጋር በመነጋገር 4ኛ ዳኛው ጨዋታውን የመምራት ሚና […]

አፍሪካ ዜናዎች

የቀድሞ የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶ የጋናው አሳንቴ ኮቶኮ አዲስ አሰልጣኝ ሆነዋል !

ፖርቱጋላዊው የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የጋና ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበሩት ማሪያኖ ባራቶን የጋናው አሣንቴ ኮቶኮ ክለብ አዲስ አሰልጣኝ  ሆነዋል።የጋናው ክለብ ከወራቶች በፊት ማክስዌል ኮናዱን ካሰናበተ በኃላ ፖርቱጋላዊውን ማሪያኖ ባራቶ በቦታው መተካቱ ሲሰማ አሰልጣኙም ወደ ጋና መድረሳቸው ታውቋል ፡፡ፖርቱጋላዊው ማርያኖ ባሬቶ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር የዋና የአሰልጣኝነት ፈቃድ ከማግኘታቸው በፊት በረዳት አሰልጣኝነት ዳይናሞ ሞስኮ ፣ […]

አፍሪካ ዜናዎች

ሲዳማ ቡና የ36 አመቱን ቤኒናዊ ግብ ጠባቂ አስፈርሟል ! – ተጨዋቹ ለብሔራዊ ቡድኑ ግዴታ ወደ ቤኒን ተጉዟል

በፈረንሣይ ቦርዶ የተወለደው እና ከ10 ክለቦች በላይ የተጫወተው ቤኒናዊው ፋቢየን ፋርኖል ለሲዳማ ቡና ፊርማውን  አካሄዶ ተጫዋቹ   ለብሔራዊ ቡድኑ ግዴታ ወደ ቤኒን ተጉዟል።በእግር ኳስ ህይወቱ ለበርካታ ክለቦች የተጫወተው እና እ.ኤ.አ በ2020 ለቱርክ ኢርዝሩምስፖር ክለብ ለመጫወት ፈርሞ ምንም ጨዋታ ያላደረገው ቤኒናዊው ግብ ጠባቂ በቀሪዎቹ የውድድር ጊዜያት ለሲዳማ ቡና ለመጫወት ተስማምቷል። በፈረንሳይ በተወለደበት ቦርዶ  ከተማ ለሚገኘው እና በዋናው […]

አፍሪካ ዜናዎች

ዋልያዎቹ በአስደናቂ የድል ዜማ ለአፍሪካ ዋንጫ ተቃርበዋል !

ዋልያዎቹ በአስደናቂ የድል ዜማ ለአፍሪካ ዋንጫ ተቃርበዋል ! በካሜሩን አዘጋጅነት  ለሚካሄደው  ቀጣይ  የአፍሪካ ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የማዳጋስካር አቻውን በ 4 ለ 0  ድል አሸንፎ ወጥቷል። የአሰልጣኝ ውበቱ አባተ ቡድን ተጋጣሚውን  በባህርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም  በሰፊ የጎል  ልዩነት ማሸነፍ ከመቻሉ በተጨማሪ በጨዋታው ብልጫም አሳይቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የጨዋታውን የመጀመሪያ ጎል በ19ኛው ደቂቃ  በአማኑኤል ገ/ሚካኤል  አማካኝነት አስቆጥሮ የማጥቃት […]

አፍሪካ ዜናዎች

ኢትዮጵያዊያን ዳኞች ታላቁን ፍልሚያ ይመሩታል !

የ2021 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ከሦስት ወራት ቆይታ በኃላ በቀጣይ ሳምንት በተለያዩ የአፍሪካ አገራት ሲቀጥል ኢትዮጵያዊያን አርቢትሮች ታላቁን ጨዋታዎችን እንዲመሩም መመረጣቸው ይታወሳል። ከዚህም መሃል በቀጣይ ሳምንት ሐሙስ የደቡብ አፍሪካዎቹ ባፋና ባፋና ከጋናዎቹ ጥቋቁር ክዋክብት ጋር በጆሀንስበርግ በኤፍኤንቢ ስታዲየም የሚያደርጉትን ወሳኝ ጨዋታ ኢትዮጵያዊያን ዳኞች ይመሩታል። ጨዋታውን በመሐል ዳኝነት ኢትዮጵያዊው ኢንተርናሽናል አርቢትር ባምላክ ተሰማ ሲመራ በረዳትነት ደግሞ […]