አትሌቲክስ ዜናዎች

ኢትዮጵያዊያን የሚሳተፉበት የቶኪዮ ኦሎምፒክ ታላቅ ፈተና ውስጥ ይገኛል !

በጃፓን በ2020 ይካሄዳል ተብሎ በኮሮና ምክንያት ለዘንድሮ የተራዘመው የቶኪዮ ኦሎፒክ አሁን ሊጀመር ቀኖቶች ሲቀሩት ዳግም ጭንቀት ውስጥ ይገኛል። በቶኪዮ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመጣው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት የጃፓን መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዛሬ ካወጀች በኋላ ከሁለት ሳምንት በኃላ በሚጀመረው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ያለ ተመልካች በዝግ ስታዲየም እንዲሆን ተወስኗል። ሐምሌ 17 የሚጀምረው የመክፈቻ ሥነ ሥርዓትም ያለተመልካች በተዘጉ በሮች […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

የሻምበል አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ  የማራቶን ውድድር ዛሬ ንጋት ላይ ተካሄዷል ! – ኢትዮ-ኤሌትሪክ የቡደን አሸናፊ ሆኗል!

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዛ ፌዴሬሽን ዛሬ  ንጋት ላይ በአዲስ አበባ ከተማ ኮዬ ፈጬ አከባቢ የ37ኛው የሻምበል አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ  የማራቶን ውድድር አካሄዷል። በውጤቱም የሴቶች አሸናፊዎች 1ኛ በሸንቄ እሙሼ ከሲዳማ ፖሊስ 2:44:51 2ኛ ፋንቱ ኢቲቻ ከኦሮ/ውሃ ስራዎች 2:45:12 3ኛ ስንቄ ደሴ ከፌደ/ማረሚያ 2:45:14 4ኛ ሰላማዊት ጌትነት ከኢት/ኤሌትሪክ 2:45:55 5ኛ ብርሀን ምህረት ከኢት/ኤሌትሪክ 2:46:37 6ኛ ፅጌሬዳ ግርማ […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

-አትሌት ሲፋን ሀሰን ለአትሌት ለተሰንበት ግደይ የእንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላለፋች !

በሄንግሎ -ኔዘርላንድ ትላንት ምሽቱን መላውን ኢትዮጵያዊያንን ያስደሰተ ድንቅ የ10ሺ ሜትር ክብረወሰን ላስመዘገበችው ጀግናዋ አትሌት ለተሰንበት ግደይ ሪከርዱን በ48 ሰአታት የተነጠቀችው በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ሆላንዳዊት አትሌት ሲፋን ሀሰን የእንኳን ደስ ያለሽ መልዕክት አስተላለፋች። አትሌት  ሲፋን ሀሰን የዓለም ክብረወሰኗን በመነጠቋ እንኳን ደስተኛ መሆኗን የሚከተለውን  ለኔዘርላንድ ኒውስላይፍ ድረ ገፅ ተናገረች ” በእንደዚህ በጣም በተቀራረበ የቀናት ልዩነት ሁለት የዓለም […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

ለተሰንበት ግደይ የ10,000 ሜትር ክብረወሰንን አስመለሰች !

  በኔዘርላንድ ሄንጌሎ ምሽቱን በተደረገ የ10ሺ ሜትር የቶኪዮ ኦሊምፒክ የማጣሪያ ውድድር ላይ ከሁለት ቀናት በፊት በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ሆላንዳዊት በሆነችው አትሌት ሲፋን ሀሰን ተሻሽሎ የነበረው እና ላለፉት 5 ዓመታት በአትሌት አልማዝ አያና ተያይዞ የነበረውን ሪከርድ በሁለት ቀናት ልዩነት በምሽቱ ውድድር ወደ ኢትዮጵያ ተመልሷል። ከቀናት በፊት አትሌት ሲፋን ሀሰን ተሻሽሎ የነበረው 29:06.82 ክብረወሰን በአትሌት ለተሰንበት ግደይ […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

” አዎ ለምን አይከፋኝም ፣ በጣም ነው የከፋኝ ! እንደውም የአለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባንዲራ ወክዬ በግሌ መሮጥ የሚል ሃሳብ ነበረኝ” – አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 

ለቶኪዮ ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን  የሚወክሉ አትሌቶችን ለመለየት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን  የማራቶን ማጣሪያ መነሻውን ሰበታ ከተማ በማድረግ 35 ኪ.ሜ ማዘጋጀቱ  ይታውሳል።   አትሌት ቀነኒሳ በቀለ  ፌዴሬሽኑ ያቅረብውን  መሰፈርት በደብዳቤ በመቃወም  ከቀናት በፊት ማሳወቁም እንዲሁ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴም ትላንት ቀነኒሳ በቶኪዮ ኦሎምፒክ ይሳተፋል በማለት  አሳውቋል። በአንፃሩ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ዛሬው ከስፖርት ዞን  የስፖርት ፕሮግራም ላይ ከጋዜጠኛ ሰኢድ ኪያር […]

Kenenisa Bekele
አትሌቲክስ ዜናዎች

” ቀነኒሳ በቀለ በኦሎፒክ ይሳተፋል ፣ ምንም ሳይረበሽ ልምምዱን ጠንክሮ ይሰራ”- ዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ

  የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቶኪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ኢትዮዽያን የሚወክሉ አትሌቶችን  ለመምረጥ ከቀናት በፊት በሰበታ የ35 ኪ.ሜ ውድድር አዘጋጅቶ በሁለቱም ፆታ መምረጡ ይታወሳል።በአንፃሩ በማራቶን ፈጣን ሰዓት ያለው የአለም ሻምፒዮኑ ቀነኒሳ በቀለ በውድድሩ ባለመሳተፉ በኢትዮዽያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ግልጽ ባልሆነ የውድድር መሥፈርት ከቶኪዮ ኦሎምፒክ የተገለለ መሥሎ የነበረ ቢመስልም ዛሬ ቀነኒሳ በቀለ በቶኪዮ ኦሎምፒክ እንደሚሳተፉ ታውቋል። የአኖካ አዲሱ ፕሬደዛንት […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

አትሌት ቀነኒሳ ያልተገኘበት ለቶኪዮ የማራቶን ምርጫ ውድድር ተካሄደ !

ለቶኪዮ 2020 በማራቶን ሀገራችንን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያዘጋጀው የማጣሪያ ውድድር ዛሬ ማለዳ በሰበታ ጎዳናዎች ተካሄዶ በሴቶትች አትሌት ትዕግስት ግርማ በወንዶች አትሌት ሹራ ቂጣታ ቀዳሚ ሆነው አሸንፈዋል። ውጤቶቹ :- በሴቶች 1ኛ ትዕግስት ግርማ 1:59:23 2ኛ ብርሀኔ ዲባባ 1:59:45 3ኛ ሮዛ ደረጄ 2:00:16 4ኛ ዘይነባ ይመር 2:03:41 5ኛ ሩቲ አጋ 2:04:28 በወንዶች 1ኛ ሹራ […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሌጎስ ማራቶን በማሸንፍ ከፍተኛውን ሽልማት አግኝተዋል !

በምዕረብ አፍሪካዊቷ ናይጄሪያ ለስድስተኛ ዛሬ ረፋድ በተካሄደው እና DSTVን  ጨምሮ ታላላቅ የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን አግኝቶ በነበረው ” Access Bank Lagos City Marathon 2021 ” የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን  ከፍተኛውን ሽልማት በማግኘት ውድድሩን አጠናቀዋል። በሴቶች የ 42 ኪ.ሜ ውድድር ኢትዮዽያዊቷ መሰረት ዲንቃ በ2:28.53 አሸናፊ በመሆን 30,000 ዶላር ተሸላሚ ስትሆን ኬኒያዊቷ ችሊስታይን ጄፕቺር በሁለተኝነት 20,000 ዶላር እንዲሁም ኢትዮጵያዊቷ […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

የ50ኛው ዓመት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል ! – ከዘጠኝ ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦለታል !

የ50ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓልን በማስመልከት የዘንድሮው ሻምፒዮናው ለየት ባለ መልኩ ዛሬ ይጀመራል። ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረኮች ያስጠሩ በርካታ አትሎቶች የሚታዮበት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዘንድሮው በተለየ ዝግጅት  ደምቆ ዛሬ ይካሄዳል ተብሏል ። የዘንድሮው ሻምፒዮና  የአገሪቱ አብዛኞቹ ክለቦች ፣ ክልሎች እና ከተሞች የሚሳተፉ ሲሆን  በኮሮና ምክንያት ያለ ተመልካች የሚካሄድም እንደሆነም ተጠቁሟል ። ዘንድሮ  ለ50ኛ […]

አትሌቲክስ ዜናዎች

ኑሯዋን በስዊዘርላንድ ያደረገቸው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አሸነፈች !

በስዊዘርላንድ ኑሯዋን ያደረገቸው እና በረጅም እና መካከለኛ ርቀቶች የግል ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ በተደጋገሚ የምታሳተፈው አትሌት ሄለን በቀለ ትላንት በጄኔቭ የሲውዝ ኦሎፒክ ኮሚቴ ባዘጋጀው የማራቶን ውድድር ላይ አሸናፊ ሆናለች። አትሌቷ የትላንቱን የማራቶን ውድድር በ2 :24.57 በመግባት ማሸነፍ ችላለች። አትሌት ሄለን በቀለ እ.ኤ.አ. በ 2005 ዓ.ም  ከ ኢትዮጵያ ወደ ጄኔቫ ስዊዘርላንድ ከገባች በኋላ ኑሯዋን  ከባለቤቷ  አትሌት […]