ዜናዎች

🏆ኢትዮጵያ ቡና የ2016 የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል!

👇
በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ከወላይታ ድቻ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒዮን መሆን ችለዋል።
የቡናማዎቹን የማሸነፊያ ግቦች ዋሳዋ ጂኦፊሪ 2x በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ ማሳረፍ ሲችል ለጦና ንቦቹ አበባየሁ ሀጂሶ አስቆጥሯል።
ኢትዮጵያ ቡና ለአመታት ተቋርጦ በዚህ አመት የጀመረውን የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር ለስድስተኛ ጊዜ ማሳካት ችለዋል።
ኢትዮጵያ ቡና የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ መሆኑን ተከትሎ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኢትዮጵያን ወክሎ በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ውድድር የሚሳተፍ ይሆናል።
@tikvahethsport