ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

“የደርቢ ጨዋታው ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ፤ደጋፊዎቻችንን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት እፈልጋለሁ ” ➖አስቻለው ታመነ

በ19ኛው ሳምንት የሸገር ደርቢ ጨዋታ ለቅዱስ ጊዮርጊስ የማሻነፊዋን ጎል አስቻለው ታመነ ጨዋታው በተጀመረ በ12ኛው ደቂቃ በጭንቀት አስቆጥሮ ጨዋታው በአስቻለው ብቸኛ ጎል ተጠናቋል። ከጨዋታው በኋላ አስቻለው ታመነ ከሱፐር ስፖርት ጋር ቆይታ አድርጓል።
በደርቢ ጨዋታ ጎል በማስቆጠሩ የተሰማው ስሜት ?
” ስሜቱ በጣም ደስ የሚል ነው። በእኔ ጎል ማሸነፋችን ደግሞ በጣም ደስ ብሎኛል ። በጣም ደስ የሚለው ደግሞ ደርቢ ላይ ስታስቆጥር ነውና የተለየ ስሜት ነው የፈጠረብኝ።
ከጨዋታው በፊት በስፑር ስፖርት በሙሉ ልብ እናሸንፋለን ብለህ ነበር : የተለየ የ9 ቀናት ዝግጅቱ ነው ለዚህ ውጤት ምክንያት ?
” አዎ …ከጨዋታው በፊት ባደረኩት ቃለ ምልልስ እንደምናሸንፍ እርግጠኛም ሆኜ ነበር። አንደኛው ዙር ላይ ያጣነውን ውጤት ለደጋፊያችን ለመካስ በሙሉ ስሜት ነበር የተነሳሳነው እና የገባነው ። ከቆየነውም የልምምድ ሁኔታ አንፃር እንደምናሸንፍ እርግጠኛ ነበርንና ያ ደግሞ ያስታውቅ ነበር የቡድኑ መንፈስም እንደምናሸንፍ እርግጠኛ ነበርኩ ለዛም ነው ከጨዋታው በፊት የተናገርኩት።
ለደጋፊዎች የሚያስተላልፈው መልዕክት ?
“የደርቢ ጨዋታው ከአዲስ አበባ ውጪ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የተካሄደው። ለደጋፊዎቻችን እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት የምፈልገው ። በቦታው ባይገኙም በቀጥታ እንደሚከታተሉ እናውቃለን በዚህ አጋጣሚ እንኳን ደስ ያላችሁ ማለት እፈልጋለሁ።
ያስቆጠርካት ጎል ለማን ትሁን ?
” ለእናቴ እና ለምወዳት ጓደኛዬ እንዲሁም ለደጋፊዎቻችን ይካፈሉት አንድም ብትሆን ትበቃለች … ( በፈገግታ)….