
በቅድሚያ እንኳን ለዒድ አልፈጥር በዓል አደረሰህ
” እንኳን አብሮ አደረሰን “
ዛሬ ሁለት ጎሎች አስቆጥረሃል ጨዋታው ኦንዴት ነበረ?
” ጨዋታው ከባድ ነበር ። ምክንያቱም እኛ አሁን እድላችን ለሁለተኛነት ስለሆነ። ከኃላም ያሉት ቡድኖች እና ከባህርዳር ጋር የተጫወትነው አንድ ነጥብ ላይ። እነሱን መራቅ ነበር የምንፈልገው እነሱም በጥንቃቄ ነበር ሲጫወቱ የነበሩት ። እኛም በጥንቃቄ ነበር ስንጫወት የነበረው። ያው አላህ አላለውም ፣ ማሸነፋችን አልቻልንም ። ያው ለቀጣይ ግን ራሳችንን አዘጋጅተን እንመጣለን”
ባለፉት ጨዋታዎች ጎል ያለማስቆጠሩ እና ጎል ሳላስቆጥር ወደ ሪከርዱም ሳልመጣ የሚል ስሜት ተሰምቶት እንደነበረ?
” በፍጹም አልተሰማኝም። ምክንያቱም እኔ በመጀመሪያ ክለባችንን ለአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ማሳለፍ የምፈልገው፤ ከጓደኞቼ ጋር ሆኜ ፣ ግን እንደዛም ሆኖ እሱንም አሳክቼ ራሴም ሪከርዱን መስበር ነው የምፈልገው፣ ቀጣይ ጨዋታዎች ራሳችንን በጥንቃቄ ተጫውተን ለአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን እና ሪከርዱንም እናሳካለን ብዬ አስባለሁ”

ዛሬ ባስቆጠረው ሁለት ጎሎች ከዮርዳኖስ አባይ ጋር እኩል መሆኑ የሚፈጥርበት ስሜት ?
” አዎ ። ምክንያቱም ዮርዳኖስ አባይ ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ከሚባሉ ትልቅ አጥቂዎች ተርታ አንደኛውና ያው እሱ ሲጫወት አላጋጠመኝም ግን በምሰማው ነገር እና አንዳንድ ቪዲዮችን በማየት ደግሞ ትልቅ ተጨዋች ነው። የእሱን ሪከርድ በመጋራቴ እንዲሁም ደውሎ አበረታቶኛልና ማመስገን እሱን እፈልጋለሁ “
ከዚህ በኃለ ባሉት ጨዋታ ስለሚያስበው ?
” ኢህሽ አላህ ፣ ከአላህ ጋር ሆኜ በሚቀጥለውም ጨዋታ እራሴን አዘጋጅቼ ለመምጣት ነው የምፈልገው። ከጓደኞቼ ጋር ሆኜ ውጤቱም ያስፈልገናልና ። ቀጣይ ጨዋታ ደግሞ ከሲዳማ ቡና ጋር ነው ፣ በጣም ከባድ ነው። ራሳችንን ለሁለተኝነት ጠንክረን እንሰራለን፣ ያሉብንን ክፍተቶች ሞልተን ሁሉም ከበረኛው እስከ አጥቂው ሁሉም ራሳችንን አዘጋጅተን እንቀርባለን ብዬ አስባለሁ”
ሁለቱ ጎሎች ለማን ይሁኑ
” ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች አንኳን አደረሳችሁ ማለት እፈልጋለሁ። ይህም ሁለት ጎሎች ለመላው የእስልምና እምነት እና ለኢትዮጵያ ስፓርት አፍቃሪዎች ማመስገን እፈልጋለሁ ፣ ለእነሱ ይሁንልኝ”
