ቤትኪንግ ፕሪሜር ሊግ ዜናዎች

“ቀጣይ ቤትኪንግ በሐዋሳ በሜዳችን መሆኑ ይጠቅመናል፣ ዘንድሮ ከሁለተኛ እስከ አራተኛ እናጠናቅቃለን እላለሁ” ➖መስፍን ታፈሰ(ሐዋሳ ከተማ )

በኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ድንቅ ብቃት እያሳየ የመጣው ወጣቱ የሐዋሳ ከተማው የፊት መስመር አጥቂ ነው።  መስፍን ታፈሰ  እንደሚታወሰው በፕሮፌሽናልነት የሙከራ ዕድል ባለፈው አመት ከወኪሉ አቶ ሳምሶን ነስሮ ጋር ወደ ኢኳቶሪያል ጊኒ ተጉዞ ልምድ አግኝቶም ተመልሷል።
መስፍን ከቅርብ ሳምንታት በጉዳት መልስ በቤትኪንግ ላይ ያለተሰለፈ ይገኛል። የቤትኪንግ በቀጣይ አዘጋጅ ሐዋሳ ከተማ ከመሆኗ አንፃር ለሐዋሳ ምን ይጠቅማል በሚል ከመስፍን ጋር ኢትዮኪክ ቆይታ አድርገናል።
ኢትዮኪክ:- ከጉዳት መልስ እንዴት ነህ?
መስፍን:- ከጉዳት መልስ አሪፍ ነኝ። ትንሽ በርግጥ ከበድ ይላል። ግን በስራ ይመጣል።
ኢትዮኪክ:- በድሬዳዋ ቡድናችሁ የተሻለ ነበር ማለት ይቻላል ? ምን የተለየ ነገር ነበር?
መስፍን:- አዎ ! በጣም የሚያስፈልገንን ውጤት ይዘናል ብዬ አስባለሁ ። ቡድኔም ጥሩ መሻሻል አሳይቷል። ይህን ደግሞ ማስቀጠል አለብን ብዬ አስባለሁ።
ኢትዮኪክ:- የቡድናቹ ጠንካራ ጎን ?
መስፍን:- የቡድናችን ጠንካራ ጎን የምለው ህብረታችን ነው። ይህን ህብረታችንን ደግሞ ማስቀጠል አለብን እላለሁ።
ኢትዮኪክ:- ዘንድሮ ለቡድንህ የምፈልገውን አድርጊያለሁ ብለህ ታስባለህ?
መስፍን:- በትንሽ አዎ። ግን ከዚህ በላይ ይጠበቅብኝ ነበረ።
ኢትዮኪክ:- ቀጣይ ሳምንት ቤት ኪንግ በሃዋሳ ከተማ ይደረጋል ፣ የሚጠቅማችሁ ነገር ይኖራል ?
መስፍን:- አዎ በቀጣይ ቤትኪንግ በሐዋሳ በሜዳችን በመሆኑ ይጠቅመናል። በጣም አሪፍ አጋጣሚ ነው ። ከእኛ የሚያስፈልገው አሁን ያለንን ህብረት በሜዳችንም ላይ ማስቀጠል የሚያስፈልገው።
ኢትዮኪክ:- የቤትኪንግ ውድድር ስንተኛ ሆነን እናጠናቅቃለን ትላለህ?
መስፍን:- እግዚአብሔር ፍቃዱ ከሆነ ከሁለተኛ እስከ አራተኛ እናጠናቅቃለን እላለሁ።ፈጣሪ ካለ ደግሞ የአፍሪካ መድረክ መካፈል ።