ዜናዎች

⭕ሽመልስ በቀለ ራሱን ከብሔራዊ ቡድን አገለለ – የአንገት ሃብል ተበርክቶለት በክብር ተሰናብቷል!

 

 

 

 

 

የዋልያዎቹ አምበል እና የመሐል ሜዳ ተጫዋች ሽመልስ በቀለ ከአስራ አምስት አመታት የብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት በኋላ ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ማግለሉን አሳውቋል።

” ጊዜው አሁን እንደሆነ ይሰማኛል ፣ ብሔራዊ ቡድኑን የምሰናበትበት ወቅት የምወደውን እና የምጓጓለትን አረንጓዴ ፣ ቢጫ እና ቀዩን ሰንደቅ አላማ ወክዬ የምጫወትበት ጊዜ
እንዳበቃ ይሰማኛል ” ሲልም በመልዕክቱ አጋርቷል።

ሀገራችንን ለሁለት አፍሪካ ዋንጫ እንድታልፍ በማድረግ ደማቅ ታሪክ እና ትልቅ አሻራን ማሳረፍ የቻለው ሽመልስ በቀለ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ 83ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ መጫወት ችሏል።

” በቀጣይም ከሀገሬ እና ብሔራዊ ቡድኑ ጎን በመሆን በስሜት እና በኩራት ዋልያዎቹን የማበረታታ መሆኑን ለመግለፅ እወዳለሁ።

ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻዋ ቀን በእኔ እምነቱ ኖሯችሁ ከጎኔ ለነበራችሁ ሁሉ ልባዊ ምስጋናዬ ይድረሳችሁ ” ሲልም ሽመልስ በቀለ በስንብት መልዕክቱ አጋርቷል።

ሽመልስ በቀለ አስራ አምስት አመታት ለኢትዮጵያ፣ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎትን ሲሰጥ የተመለከተው አንድ የቢጫ ካርድ ብቻ ነው።

የዋልያዎቹ አማካይ የነበረው ሽመልስ በቀለ ከብሔራዊ ቡድኑ መሠናበቱን ዛሬ ይፋ ካደረገ በኃላ የስንብት ስነስርዓት የኢትዮጵያ እ/ፌ/ፕ ተዘጋጅቶለት የአንገት ሃብል ተበርክቶለት በክብር ተሰናብቷል።
⭕የሽልመልስ የ15 ዓመት የብሔራዊ ቡድኑ ቆይታ እና  ቁጥሮች

8⃣3⃣ – የጨዋታ ብዛት

1⃣6⃣ – ጎሎች

1⃣3⃣ – ለጎል የሚሆኑ ኳሶች

1⃣ – ቢጫ ካርድ

0⃣ – ቀይ ካርድ

 

 

#አዲሱ የቲክቶክ ገፃችን

tiktok.com/@ethiokick

#በቴሌግራም :-

https://t.me/Ethio_Kickoff

#በኢንስታግራም ገጻችንን :-

https://www.instagram.com/ethio_ki

🔛ድረ ገጻችንን :-

Home page