ዜናዎች

– የኢትዮዽያ ብሔራዊ ቡድን በ7 ጎሎች አሸነፈ!

ከሐምሌ 10 እስከ 25/2013 ዓ.ም ድረስ በ11 የሴካፋ አባል አገራት መካከል በባህር ዳር ከተማ ለሚካሄደው ከ23 ዓመት በታች የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገራት ውድድር የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች የወዳጅነት ጨዋታ ዛሬም አድርጓል።የኢትዮጵያ ከ 23 ዓመት በታች በቅርቡ ለሚጠብቀው የሴካፋ ሻምፒዮና በአዳማ አበበ በቂላ ስታዲየም ዛሬ ባደረገው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ የአዳማ ከተማ ወጣት ቡድንን 7 ለ 1 አሸንፏል።
ከ 23 ዓመት በታች ብሔራዊ በድኑ በቅርቡ ከመድን ጋር የወዳጅነት ጨዋታ አካሄዶ እንዲሁ ማሸነፉ ይታወሳል።ቡድኑ የወዳጅነት ጨዋታ ማድረጉ ጥሩ ቢሆንም የወዳጅነት ጨዋታ የሚደርገቻው ክለቦችን  ከምን አንጻር አሰልጣኞቹ መምረጣቸው አሁን ላይ ባይታወቅም በቀጣይ ወድድሩ ሲጀመር ግን ሊያስተቸው እንደሚችል ይገመታል።
📸TIKVAH