ዜናዎች

# አሰልጣኝ አስራት ኃይሌን የከተማው አመራሮች በቤቱ ተገኝተው ጠይቀዋል! -የ250ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ አመራሮች እና ሰራተኞች ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ እግር ኳስን በታማኝነት ላገለገለው አንጋፋው አሰልጣኝ አስራት ኃይሌ (ጎራዴው) ለሕክምና ወጪ የሚውል የ250ሺ ብር ድጋፍ አድርገው በመኖርያ ቤቱ ጠይቀውታል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ባስተላለፉት መልዕክት በሴካፋ ያመጣው ድል በእግር ኳስ ፌድሬሽን በሰጠው አመራርነት በርካታ አሰልጣኞችን በማፍራት የሚታወቀውን አስራት ኃይሌ በማገዛችን ትልቅ ክብር ይሰማናል ብለዋል።
የኢትዮጵያን እግር ኳስን በታታሪነት ያገለገለውን አስራትን ለማሳከም የስፓርት ቤተሰቡ ርብርብ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን ያቀረቡት ቢሮ ኃላፊው የጥንካሬ ተምሳሌት የሆነው አሰልጣኝ አስራት ኃይሌ ሕክምናው ጨርሶ አገሩን እንዲያገለግል እግዚአብሔር ምሕረቱን እንዲሰጠው መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ ብለዋል
🔛የስፖርት ቤተሰቡን አፋጣኝ ድጋፍ የሚጠበቀውን አሰልጣኝ አሰራት ሃይሌ የህክምና ድጋፍ ለማድረግ
የአካውንት ቁጥሮቹ:-
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000544405617
ንብ ባንክ 7000043195037